Your browser doesn’t support HTML5
በኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ትኩረት ሳያደርጉ ዘለቄታ ያለው ልማት ማምጣት የማይቻል መሆኑን በያዝነው ወር ይፋ የሆኑ ሁለት የጥናት ዘገባዎች አመለከቱ። ለጋሽ አገሮች የሚሰጡት ገንዘብ የመብት ጥሰትን ለማባባስ ያለመዋሉን የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለባቸው ሪፖርቱ ይጠይቃል።
የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በበኩላቸው በሕዝቧ ቁጥር በአፍሪቃ በሁለተኛ ደረጃ ላይ በምትገኘው ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በእጅጉ ተንተሰራፍቷል። በመሆኑም “ለጋሽ አገሮች የሚሰጡት ገንዘብ በዜጎች ላይ በሚፈጸመው የመብት ጥሰት መባባስ የሚኖረውን ሚና መመርመር መቻል አለባቸው፤” ነው የሚሉት።