የአርቲስት ሃጫሉን ግድያ ተከትሎ በሰብዓዊነት ላይ ወንጀል የፈፀሙ ሕግ ፊት እንዲቀርቡ ኢሰመኮ ጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል የተፈፀመው ድርጊት በሰብዓዊነት ላይ የተፈፀመ ወንጀል ነው ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ዛሬ የምርመራ ውጤቱን ይፋ ሲያደርስግ በዚህ አሰቃቂ ባለው ድርጊት በአጠቃላይ የ123 ሰዎች ሕይወት ማለፉንም ገለፀ።