ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከሊቢያ እስር ቤት አመለጡ

Your browser doesn’t support HTML5

በሊቢያ የእርስ በእርስ ጦርነት እየተባባሰ በመምጣቱና ያለጠባቂ በመተዋቸው ምክንያት ግንብ ንደው ከመጠለያው እንዳመለጡ 30 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ለቪኦኤ ገለፁ። ከጦርነት ቀጠና ሸሽተው አሁን ያሉበት ቢደርሱም በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሚገኙ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በፍጥነት ወደ ሃገራችን እንዲመልሰን እንማፀናለንም ብለዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስደተኞቹን ወደ ሃገር ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ እንደሆነ ገልፀዋል።