የምርጫው ዝግጅት ገፅታ

  • ሔኖክ ሰማእግዜር

አዲስ አበባ

Your browser doesn’t support HTML5

የምርጫው ዝግጅት ገፅታ

“ግንቦት 16 / 2007 ዓ.ም ከሚካሄደው ሃገር አቀፍና የክልል ምክር ቤቶች ምርጫ አስቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ ጎዳናዎች በገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ የምርጫና የማስተዋወቂያ ሠሌዳዎች ተሞልታለች” ይለናል ምርጫውን ለመዘገብ ኢትዮጵያ የሚገኘው ሔኖክ ሰማእግዜር።

“መጭው ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ ነው” የሚል መልዕክት የሠፈረባቸው የማስታወቂያ ሠሌዳዎች በከተማይቱ ዋና ዋና ጎዳናዎችና አደባባዮች በብዛት እንደሚታዩ ዛሬ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ተዘዋውሮ መመልከቱን አመልክቷል፡፡

ተቃዎሚ ፓርቲዎች በበኩላቸው ይህን መሰሉን ግዙፍ የማስታወቂያ ሰሌዳዎች ቀርቶ ትናንሽ ፖስተሮችን ለማሣተምና ከምርጫው በፊት ለማሠራጨት መቸገራቸውን ነው የሚናገሩት።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡