"እዚሁ እንቆይ ወይስ ወደመጣንበት እንመለስ?" - የኢትዮጵያ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጭንቀት

Your browser doesn’t support HTML5

በሰሜን ኢትዮጵያ አፋር ክልል የሚገኙ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ከአንዳንዶቹ የመጠለያ ካምፖች በምግብ እና በመጠለያ ዕጥረቱ የተነሳ ወደመጡበት ተመልሰዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተፈናቃዮቹ ወደመጡበት ቀያቸው ቢመለሱ የተሻለ ሁኔታ ላይጠብቃቸው እንደሚችል በመግለጽ ሲያስጠነቅቅ ቆይቷል።

ተጨማሪ ዓለም አቀፍ ዕርዳታ እንዲቀርብላቸውም ተማጽኗል።

/ሃሊማ አቱማኒ ከሰመራ ያጠናቀረችውን ዘገባ ቆንጅት ታየ ወደ አማርኛ መልሳዋለች/