የሠላም ሥምምነቱ ሊካሄድ ለታቀደው አገራዊ ምክክር አወንታዊ ሚና ይጫወታል ተባለ

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ መንግሥትና በህወሓት መካከል የተደረሰው የሠላም ሥምምነት የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክረ ኮሚሽን ሊያካሂደው ላሰበው ህዝባዊ ምክክር የሚኖረው አስተዋጽኦ የላቀ ነው ሲሉ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ አስታውቀዋል።

ኮሚሽነሩ ልዩነትን በጠመንጃ አፈሙዝ ሳይሆን በውይይት የመፍታት ባህል መጎልበት አለበት ሲሉም መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

በተያያዘ ዜና የሠላም ሥምምነቱን ተከትሎ የእርዳታ መኪናዎችን ወደ መቀሌ እና ሽሬ ለመላክ የሰብዓዊ ተቋማት ከመንግሥት ጋር እየተነጋገሩ መሆኑነን የተባበሩት መንግሥታት ገልጿል።