“አይዞሽ ደስ ይበልሽ! ለመገናኘት ደግሞ ያብቃን” - የአትሌት ጎተይቶም እናት

Your browser doesn’t support HTML5

በዩናይትድ ስቴትስ ዩጂን - ኦሬገን ላይ እየተካሄደ ባለው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፕዮና በሴቶች ማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ያሸነፈችው አትሌት ጎተይቶም እናት በውጤቱ መደሰታቸውን ገልፀው ለልጃቸው ከትግራይ ክልል መልዕክት አስተላልፈዋል።

እንደርታ ወረዳ ማይቀያህ በምትባል መንደር ነዋሪ የሆኑት የአትሌቷ እናት ወ/ር በረኽይቱ ካሳ፤ ከዚህ ቀደም ስታሸንፍ ስልክ ደውላ እንደምታነጋግራቸው አሁን ግን ካነጋግሯት ሰባት ወራት መቆጠሩን ገልፀው፤ “አይዞሽ ደስ ይበልሽ! ለመገናኘት ደግሞ ያብቃን” በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።