እንደገና የሞቀው የኢትዮጵያና የኤርትራ የድንበር ጉዳይ እሰጥ አገባ

ኢትዮጵያና ኤርትራ

Your browser doesn’t support HTML5

እንደገና የሞቀው የኢትዮጵያና የኤርትራ የድንበር ጉዳይ እሰጥ አገባ - ዘገባ

ከአምባሣደር ግርማ አስመሮም ጋር ለተደረገው ቃለምልልስ ከታች ያለውን የድምፅ ፋይል ከፍተው ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

አምባሣደር ግርማ አስመሮም በኢትዮጵያና በኤርትራ ጉዳይ ከቪኦኤ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

አምባሣደር ዲና ሙፍቲ ከቪኦኤ የትግርኛ ዝግጅት ክፍል ባልደረባ በትረ ሥልጣን ጋር ያደረጉትን ውይይት ከታች ከተቀመጠው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

አምባሣደር ዲና ሙፍቲ በኢትዮጵያና ኤርትራ ጉዳይ ከቪኦኤ ጋር ያደረጉት ውይይት

የኤርትራ መንግሥት ኢትዮጵያ ጦሯን “ከተወሰነልኝ ክልል ታስወጣ” እያለ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ባለፈው ሣምንት ለፓርላማቸው ባደረጉት ንግግር የኤርትራ መንግሥት “የአካባቢውን ሰላም በማደፍረስ ቀጥሏል” ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሣምንቱ ማብቂያ ጅቡቲን በጎበኙበት ወቅት የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማይል ኦማር ጊሌም በኤርትራ ላይ ተመሣሣይ ክሥ አሰምተዋል፡፡

በአፍሪካ ኅብረት የኤርትራ ቋሚ ተጠሪ፤ አምባሣደር አርአያ ደስታ ሰሞኑን ለኅብረቱ የወቅቱ ሊቀመንበር ሮበርት ሙጋቤ ደብዳቤ ፅፈው በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ያለው የድንበር ጉዳይ በሕግም ሆነ በቴክኒክ ውሣኔ ካገኘና ከተጠናቀቀ ሰባት ዓመታት ማለፋቸውን፤ የኢትዮጵያ ጦር ከኤርትራ ግዛት እንዲወጣና መሬቱ እንዲመለስላቸው ግፊት እንዲደረግ ጠይቀዋል፡፡

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኤርትራ አምባሣደር ግርማ አስመሮምም ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ተመሣሣይ ጥያቄ አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ አምባሣደር ዲና ሙፍቲ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ የድንበር ኮሚሽኑን ውሣኔ መቀበሏን በወቅቱ ማሳወቋን ጠቁመው የመካለሉን ጉዳይ ለመጨረስ ኤርትራ ለውይይት መቀመጥ እንዳለባት ተናግረዋል፡፡

ለዘገባው ከላይ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡