ከኢህአዴግ ጋር ለመደራደር የወሰኑት 12ቱ ተቃዋሚ ድርጅቶች የጋራ ስብስብ ፈጠሩ

  • መለስካቸው አምሃ
ለአለፉት ሰባት ወራት ያህል ከገዥው ግንባር ኢህአዴግ ጋር ውይይት እና ድርድር ሲያደርጉ ከቆዩት ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል አሥራ ሁለቱ ወደ ፊት ለሚደረግ ድርድር አንድ የጋራ ስብስብ መፍጠራቸውን ይፋ አደረጉ፡፡

ለአለፉት ሰባት ወራት ያህል ከገዥው ግንባር ኢህአዴግ ጋር ውይይት እና ድርድር ሲያደርጉ ከቆዩት ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል አሥራ ሁለቱ ወደ ፊት ለሚደረግ ድርድር አንድ የጋራ ስብስብ መፍጠራቸውን ይፋ አደረጉ፡፡ ስብስቡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በአንድነት ሆነው ጠንካራ የመደራደሪያ ሀሳቦች ለማቅረብ የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል፡፡

አሥራ ሁለቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መስርተነዋል ባሉት ስብስብ ላይ ማብራሪያ የሚሰጥ ጽሑፍ አሰራጭተዋል፡፡ ጽሑፉ እንደሚያስረዳው ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ በሀረገሪቱ የፖለቲካ ሥርዓት ውስጥ ለውጥ ለማምጣት ወሳኝ ሚና መጫዎች እንዳለባቸው እምነታቸው ነው፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ከኢህአዴግ ጋር ለመደራደር የወሰኑት 12ቱ ተቃዋሚ ድርጅቶች የጋራ ስብስብ ፈጠሩ