በመቐለ የዒድ አከባበር ሕዝበ ሙስሊሙ ተፈናቃዮችን እንዲያስብ ተጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

በመቐለ ከተማ በድምቀት በተከበረው 1ሺሕ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ላይ የተገኙ ታዳሚዎች፣ በዓሉንን፣ በተስፋ እያከበሩት እንደኾነ ገልጸዋል፡፡

የትግራይ ክልል የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼኽ አደም ዓብደልቃድር ጁሃር፣ "የዘንድሮ ዒድ አልፈጥር በዓል፣ ካለፉት ዓመታት በተሻለ ሰላም እና ተስፋ እየተከበረ ያለ በዓል ነው፤" ብለዋል፡፡

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው፣ ሕዝበ ሙስሊሙ፣ በክልሉ መልሶ ግንባታ ሒደት ላይ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።