ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ብርሃኑ ፀጋዬ ከቪኦኤ ጋር

አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ /የኢትዮጵያ ፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ/ ፎቶ ፋይል - ኅዳር 3/2011 ዓ.ም - አዲስ አበባ/

የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ተጠናቅቆ በመጭው ሣምንት ውስጥ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ አስታውቀዋል።

የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ተጠናቅቆ በመጭው ሣምንት ውስጥ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ አስታውቀዋል።

የአቃቤ ሕግ መሥሪያ ቤት በሕዝብ የታመነ እንዲሆንና ለሕግ የበላይነት መከበር እንዲሠራ እንዲሁም ነፃነቱ የተጠበቀ መሆኑን ለማረጋገጥ የአማካሪዎች ምክር ቤት ማቋቋምን ጨምሮ እየተሠሩ ናቸው ያሏቸውን ተግባራት ፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ልዩ ቃለ-ምልልስ አመልክተዋል።

“ለለውጥ የተጀመረው ሂደት የፖለቲካ አቅጣጫ እየያዘ ነው” ሲሉ የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት የሰጡትን መግለጫ “ለፖለቲካ ፍጆታ የተባለ” ብለውታል። መሥሪያ ቤታቸው ሰዎችን የሚያየው “በፖለቲካ ማንነታቸው ሳይሆን በፈፀሙት ተግባር ነው” ብለዋል።

ከጠቅላይ አቃቤ ሕግ ብርሃኑ ፀጋዬ ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለ-ምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ብርሃኑ ፀጋዬ ከቪኦኤ ጋር