በየሄዱባቸው ሃገሮች የሁለት ሣምንት ሥልጠናቸውን አጠናቅቀዋል፡፡
አዲስ አበባ - ዋሺንግተን ዲሲ —
Your browser doesn’t support HTML5
ኢትዮጵያ ውስጥ ኢቦላ እስከአሁን እንደሌለ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አቤል የሻነህ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡
ይሁን እንጂ በተለያዩ ቋንቋዎች የተሰናዱ ተጨማሪ የቅስቀሣ ቁሳቁስ ሕትመት መጠናቀቁንና ወደ ክልሎች ለማከፋፈል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ወደ ምዕራብ አፍሪካ የዘመቱ የጤና ባለሙያዎችም የሁለት ሣምንታት ሥልጠና አጠናቅቀው በየሙያቸው ለመሠማራት እየተዘጋጁ መሆናቸውን አቶ አቤል አመልክተዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡