የምስራቅ ሸዋ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

በኦሮምያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌና ቦሰት ወረዳዎች መንግሥት ሸኔ በሚለው እና ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ብሎ በሚጠራው ቡድን ተፈጸመ ባሉት ጦቃት የተፈናቀሉ ዜጎች ወደቀያቸው እየተመለሱ ነው ሲል የዞኑ ፖሊስ አስታወቀ።

በመስከረም ወር ተፈጸመ በተባለው ጥቃት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተፈናቅለው ወደ ደቡብ ክልል መሰደዳቸውን በሃዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ እና በካምባታ ዞን የተጠለሉ ተጎጂዎች ለአሜሪካ ድምፅ በስልክ ገልፀዋል።

ተፈናቂዎቹ አክለውም የመተሃራ እና አካባቢው ጥቃት የፈጸመው ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው እና የኢትዮጵያ ፓርላማ ግን ሸኔ በሚል በአሸባሪነት የፈረጀው ቡድን ነው ይላሉ። በጥቃቶቹ 14 ሰዎች መገደላቸውንም ተናግረዋል።