የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤርትራ የቀረበበትን ክስ አሰተባበለ

Your browser doesn’t support HTML5

የኤርትራ ሲቪል አቭዬሽን ያቀረበበትን ክስ፣ “ስም የማጥፋት ሥራ ነው” ሲል የተቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ አቭዬሽኑ የበረራ እገዳ ውሳኔውን ዳግም እንዲያጤነው ጠይቋል፡፡

የኤርትራ ሲቪል አቭዬሽን፣ በአገሪቱ ጋዜጣ ላይ ታትሞ በማኅበራዊ የትስስር ገጾች ላይ በተሰራጨ የእግድ ትእዛዙ፣ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ የተለያዩ ክሶችን አቅርቦ፣ አየር መንገዱ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ፣ ከመጪው መስከረም 20 ቀን ጀምሮ እንዲቋረጥ መወሰኑ ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ ትላንት ሰኞ፣ ለጋዜጠኞች መግለጫ በሰጡበት ወቅት፣ የኤርትራ ባለሥልጣናት “ውሳኔያቸውን እንደገና ያዩታል ብለን ተስፋ እናደርጋለን፤” ብለዋል፡፡