"ለስድስት ወራት ድጋፍ ስላላገኘን ለችግር ተጋልጠናል" - ተፈናቃዮች

ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ በሎ ጀገንፎይ የተመለሱ አንዳንድ ተፈናቃዮች ለስድስት ወራት ድጋፍ ስላላገኘን ለችግር ተጋልጠናል ሲሉ ተናገሩ።
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በወረዳው ቢከሰት ክፉኛ ሊጎዳቸው እንደሚችልም ስጋታቸውን ገልፀዋል።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ አደጋ ስጋት አመራር ፅህፈት ቤት ኃላፊ በበኩላቸው ድጋፎቹ በመንግሥት እየተደረጉ ነው በፍትሃዊነት ለሚያስፈልገው ማሰራጨት ላይ ችግር አለ ብለዋል።
የክልሉ መንግሥት ችግሩ እንዲፈታ አቅጣጫ እንደሰጠና ካልሆነም ዕርምጃ እንደሚወሰድ ገልፀዋል።
የኦሮምያ ክልል አደጋ ስጋት ቢሮ በበኩሉ ድጋፍ የሚሹ ሰዎችን ለይተው ድጋፍ ለማድረግ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

"ለስድስት ወራት ድጋፍ ስላላገኘን ለችግር ተጋልጠናል" - ተፈናቃዮች