የድጋፍ ሰልፍ፣ የእግር ጉዞና የደም ልገሳ በድሬዳዋ

Your browser doesn’t support HTML5

የድሬዳዋ አስተዳደር ነዋሪዎች ከመከላከያ ሰራዊቱ ጎን መቆማቸውን ለማሳየት የእግር ጉዞና የደም ልገሳ አካሂደዋል።
በሺሕ የሚቆጠሩ የከተማዋ ነዋሪዎችና መንግሥት ሰራተኞች በተሳተፉበት የእግር ጉዞ ማጠቃለያ ላይ ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ የአስተዳደሩ ነዋሪ ግንባር በመዝመት ብቻ ሳይሆን በየተሰማራበት ሙያ በሃላፊነት ስሜት አገልግሎት በመስጠት የመከላከያ ደጀን መሆኑን ማስመስከር ይተበቅበታል ብለዋል።
የእግር ጉዞው ተሳታፊዎች በሚችሉት ሁሉ የመከላከያ ሰራዊትን እንደሚደግፉ ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።