የኢድ አልፈጥር በዓል አከባበር በድሬዳዋ

Your browser doesn’t support HTML5

1443ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በድሬዳዋ ኢድሜዳ በሰላም ተከብሯል። ጎንደር ላይ በሙስሊሞች ላይ ተፈጽሟል የተባለውን ጥቃት ለመቃወም በሚል መነሻነት ባለፈው አርብ ድሬዳዋ ላይ ተከስቶ የነበረው ግጭት ሙስሊሙን ማኅበረሰብ አይወክልም ተብሏል። የከተማዋ ክርስትያን በጎ ፈቃደኞች ከስግደት ለተመለሱ ሙስሊም ምዕመናን ውሃና ጣፋጭ ምግቦችን ያዘጋጁ ሲሆን የሌሊት ታክሲ ማኅበር አባላትም ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጥተዋል።