ደብረ ብርሃን የሚገቡ ተፈናቃዮች ቁጥር እየጨመረ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር አሁን ባለው አደረጃጀትና አነስተኛ መሰረተ ልማት ተጨማሪ ተፈናቃዮችን ማስተናገድ በማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን አስታወቀ።

በአንጻሩ በፀጥታ መደፍረስ ምክኒያት ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው ወደ ደብረ ብርሃን የሚመጡ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑ ተገልጿል።

ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው ከተማዋ ውስጥ ባሉ መጠለያ ጣቢያዎች የተጠለሉት ሰዎቸ ቁጥር 28 ሺህ መድረሱን ያመለከተው የከተማ አስተዳዳሩ ለተፈናቃዮቹ ተገቢው ትኩረት እንዳልተሰጠ ገልፆ ቅሬታ አቅርቧል፡፡

በመጠለያ ጣቢያዎቹ የተጠለሉ ተፈናቃዮችም በቂ የምግብ ድጋፍ እያገኙ እንዳልሆነ ገልፀዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።