የትግራይ ኃይሎች ከአፋር ወጥተናል ማለታቸውን የመንግሥት ባለሥልጣናት አልተቀበሉትም

Your browser doesn’t support HTML5

የትግራይ ኃይሎች ጦራቸውን ከአጎራባች የአፋር ክልል አካባቢዎች አስወጥተናል በሚል ያቀረቡትን ገለፃ የኢትዮጵያ ፌዴራል ባለሥልጣናት ውድቅ እያደረጉት ነው።

የህወሓት ቃል አቀባይ በያዝነው ሳምንት በሰጡት አስተያየት በክልሉ ለሚገኙ ተረጂዎች የሚፈለገው የምግብ እርዳታ ትግራይ ይደርስ ዘንድ የፌዴራሉ መንግሥት እንዲፈቅድ አማፅያኑ ኃይሎቻቸውን ማስወጣታቸውን ተናግረዋል።

ሄንሪ ዊልኪንስ ከሐይቅ ለአሜሪካ ድምፅ ያጠናቀረውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።