ኢትዮጵያ ሦስተኛው የኮቪድ ማዕበል አስግቷል

  • መለስካቸው አምሃ

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ የኮቪድ ወረርሽኝ ሦስተኛው ማዕበል እየጀመረ መሆኑን የሚጠቁሙ ምልክቶች እየታዩ ናቸው ሲል የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት አስታወቀ። ዴልታ የተሰኘው አዲሱ የኮቪድ-19 ዝርያ በሃገሪቱ መኖር አለመኖሩን በቅርቡ እንደሚያረጋግጥም ገለፀ። ወደ 22 ለሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በስድስት ወር ውስጥ የኮቪድ ክትባትን ለማዳረስም እየተሠራ ነው ተባለ።