የኮቪድ ክትባት በኢትዮጵያ
Your browser doesn’t support HTML5
ኢትዮጵያ በ2013 ዓ.ም ሚያዝያ ወር መጨረሻ ላይ ዘጠኝ ሚሊዮን ፀረ ኮቪድ-19 ክትባት ወደ ሀገር ለማስገባት እየሰራች መሆኗን አስታወቀች ። የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ለአሜሪካ ድምፅ እንደገለፀው እስከ 2013 ዓመት መጨረሻ ከአጠቀላይ የኢትዮጵያ ህዝብ 20 ፐርሰንት የሚሆኑት ክትባቱን እንዲያገኙ እየተሰራ ነው።