በኢትዮጵያ ኮቪድ 19 እየተባባሰ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ውስጥ በኮቪድ 19 ምክንያት የደረሰው የህይወት ጉዳት 1706 መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የሚኒስቴሩ የኮምዩኒኬሽንስ ዳይሬክተር ዶ/ር ተገኔ ረጋሳ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃል የዛሬን መረጃ ሳይጨምር ሦስት መቶ ሰዎች የፅኑ ህመም ህክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ገልፀዋል።