ጣልያን ሚላን ከተማ ባቡር ተገልብጦ የሦስት ሰዎች ሕይወት አለፈ

Your browser doesn’t support HTML5

ጣልያን አገር ውስጥ ከሚላን ከተማ ወጣ ብሎ አንድ ባቡር ተገልብጦ ሦስት ሰዎች ሞተው ሌሎች አሥር በጠና መቁሰላቸው ታወቀ። አደጋው ዛሬ ሐሙስ የደረሰው፣ ከሴርሞና ከተማ ወደ ሚላን ያመራ በነበረው የመንገደኞች ባቡር ላይ ሲሆን፣ ሰገሬት ከተማ ሲቃረብ ነው የመካከለኞቹ ፉርጎዎች ከሀዲዱ ሊወጡና ሊገለበጥ የቻለው። የአደጋ መከላከልና አስወጋጅ ቡድን ወደ ስፍራው በመሄድ ለቆሰሉት መንገደኞች እርዳታ ማድረጉም ታውቋል።