ቻይና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ እንደምትሾም አስታወቀች

Your browser doesn’t support HTML5

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ቤጂንግ በቅርቡ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ልዩ ልዑክ እንደምትልክ ይፋ አደረጉ፡፡ በኬኒያ በጉብኝት ላይ የሚገኙት ዋንግ መግለጫ የተሰማው ከአንድ አመት በላይ የዘለቀው የኢትዮጵያ ጦርነትን ተከትሎ የዩናይትድ ስቴትስ የምስራቅ አፍሪካ ልዩ ልዑክ ሃሙስ ዕለት ኢትዮጵያ ሲገቡ ነበር፡፡