በካሜሩን ሴቶች በጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ ጦሩ ያሰራቸው ወጣቶች ተለቀቁ

Your browser doesn’t support HTML5

የካሜሩን ወታደራዊ ኃይል በአማፂነት ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር አውሏቸው የነበሩ ሰላሳ ወጣቶችን ለቀቀ። ጦሩ እርምጃውን የወሰደው የታሳሪዎቹን ወላጆች ጨምሮ በመቶዎች የተቆጠሩ ሴቶች የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው።

ከደቡብ ምዕራቧ የኢኮና ከተማ የመጡት እነኚህ ሴቶች ‘በክልሉ የመብት ጥሰት ፈጽሟል’ ሲሉ የካሜሩንን ጦር ሰራዊትን ከሰዋል። ጦሩ ውንጀላውን አስተባብሏል።