ከሣምንታት በፊት ባካሄደው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ የቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ አላገኙም ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ነሐሴ 26 / 2005 ዓ.ም ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን አስታውቋል።
አዲስ አበባ —
ከሣምንታት በፊት ባካሄደው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ የቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ አላገኙም ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ነሐሴ 26 / 2005 ዓ.ም ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን አስታውቋል።
ፓርቲው ዛሬ በሰጠው መግለጫ መንግሥት ለጥያቄዎቹ ትኩረትም አለመስጠቱን ገልጿል።
ሰማያዊ ፓርቲ ከ1997ቱ ምርጫ ወዲህ በዓይነቱ የመጀመሪያ የተባለውን የተቃውሞ ሰልፍ ያካሄደው ግንቦት 25/2005 ዓ.ም እንደነበር ይታወሣል፡፡
በዚሁ ሠልፍ ላይ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እንዲስተካከሉ፣ የፖለቲካ እና የሕሊና እሥረኞች እንዲፈቱ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች ጣልቃ መግባት እንዲቆም እና የተፈናቃሉ ዜጎች ወደቀያቸው እንዲመለሱ ጠይቆ መንግሥት ለጥያቄዎቹ ምላሽ ካልሰጠውም ከሦስት ወራት በኋላ ሌላ ሰልፍ እንደሚጠራ አስታውቆ ነበር፡፡
የሰማያዊ ፓርቲን ጋዜጣዊ መግለጫ የተከታተለው እስክንድር ፍሬው ከአዲስ አበባ ያደረሰን ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል፤ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡት።
Your browser doesn’t support HTML5
ሰማያዊ ፓርቲ ሌላ ሰልፍ ጠራ
ከሣምንታት በፊት ባካሄደው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ የቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ አላገኙም ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ነሐሴ 26 / 2005 ዓ.ም ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን አስታውቋል።
ፓርቲው ዛሬ በሰጠው መግለጫ መንግሥት ለጥያቄዎቹ ትኩረትም አለመስጠቱን ገልጿል።
ሰማያዊ ፓርቲ ከ1997ቱ ምርጫ ወዲህ በዓይነቱ የመጀመሪያ የተባለውን የተቃውሞ ሰልፍ ያካሄደው ግንቦት 25/2005 ዓ.ም እንደነበር ይታወሣል፡፡
አቶ ይልቃል ጌትነት - የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር
በዚሁ ሠልፍ ላይ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እንዲስተካከሉ፣ የፖለቲካ እና የሕሊና እሥረኞች እንዲፈቱ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች ጣልቃ መግባት እንዲቆም እና የተፈናቃሉ ዜጎች ወደቀያቸው እንዲመለሱ ጠይቆ መንግሥት ለጥያቄዎቹ ምላሽ ካልሰጠውም ከሦስት ወራት በኋላ ሌላ ሰልፍ እንደሚጠራ አስታውቆ ነበር፡፡
የሰማያዊ ፓርቲን ጋዜጣዊ መግለጫ የተከታተለው እስክንድር ፍሬው ከአዲስ አበባ ያደረሰን ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል፤ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡት።