ሰማያዊ ፓርቲ ሌላ ሰልፍ ጠራ

  • እስክንድር ፍሬው

ሰማያዊ ፓርቲ

ከሣምንታት በፊት ባካሄደው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ የቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ አላገኙም ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ነሐሴ 26 / 2005 ዓ.ም ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን አስታውቋል።



Your browser doesn’t support HTML5

ሰማያዊ ፓርቲ ሌላ ሰልፍ ጠራ


ከሣምንታት በፊት ባካሄደው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ የቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ አላገኙም ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ነሐሴ 26 / 2005 ዓ.ም ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን አስታውቋል።

ፓርቲው ዛሬ በሰጠው መግለጫ መንግሥት ለጥያቄዎቹ ትኩረትም አለመስጠቱን ገልጿል።

ሰማያዊ ፓርቲ ከ1997ቱ ምርጫ ወዲህ በዓይነቱ የመጀመሪያ የተባለውን የተቃውሞ ሰልፍ ያካሄደው ግንቦት 25/2005 ዓ.ም እንደነበር ይታወሣል፡፡

አቶ ይልቃል ጌትነት - የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር


በዚሁ ሠልፍ ላይ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እንዲስተካከሉ፣ የፖለቲካ እና የሕሊና እሥረኞች እንዲፈቱ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች ጣልቃ መግባት እንዲቆም እና የተፈናቃሉ ዜጎች ወደቀያቸው እንዲመለሱ ጠይቆ መንግሥት ለጥያቄዎቹ ምላሽ ካልሰጠውም ከሦስት ወራት በኋላ ሌላ ሰልፍ እንደሚጠራ አስታውቆ ነበር፡፡

የሰማያዊ ፓርቲን ጋዜጣዊ መግለጫ የተከታተለው እስክንድር ፍሬው ከአዲስ አበባ ያደረሰን ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል፤ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡት።