ብሊንከን ለምዕራብ እና መካከለኛ አፍሪካ ይፋ ያደረጉት ድጋፍ

Your browser doesn’t support HTML5

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፣ በኒጀር ጉብኝታቸው፣ አሜሪካ ለምዕራብ እና መካከለኛ አፍሪካ፣ የ150 ሚሊዮን ዶላር ሰብአዊ ድጋፍ እንደሚሰጥ ይፋ አድርገዋል። የአፍሪካ ጉዟቸውን በመቀጠል፣ ትላንት ከኢትዮጵያ ወደ ኒጀር ያመሩት፣ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፣ ከጸጥታ ጋራ በተገናኘ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው አፍሪካ ለተፈጠረው ሰብአዊ ቀውስ የሚውል የ150 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።