ባይደን የመራጮች ሕግ ከግዛቶች ይልቅ በፌደራል መንግስት እንዲወሰን ጫና እያደረጉ ይገኛሉ

Your browser doesn’t support HTML5

ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን የመራጮች መብት መከበር የአሜሪካዊያን እሴት በመሆኑ ሊከበር ይገባል ሲሉ ምርጫን የሚገድቡ ሕጎች በግዛቶች እንዳይወጡ ሕግ እንዲጸድቅ እየጣሩ ይገኛሉ፡፡ በአንጻሩ ተቀናቃኞቻቸው ሪፐብሊካኖች የምርጫ መጭበርበርን እና የምርጫ ኮሮጆ ደህንነትን ለማስጠበቅ ጥብቅ የሆነ የመራጮች ማንነት ማረጋገጫ ሊቀርብ ይገባል በማለት እየተከራከሩ ይገኛሉ፡፡