ቤህነን አንድ አባሉ በፀጥታ ኃይሎች መገደሉንና ሰባት ሰው መቁሰሉን አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

የቤኒሻንጉል ሕዝብ ነጻነት ንቅናቄ (ቤህነን) የፖለቲካ ድርጅት አንድ አባሉ በጸጥታ ኃይሎች መገደሉና ሰባት ሰው መቁሰሉን አስታወቀ።

ድርጊቱ የተፈፀመውም የፓርቲው ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አከፋፈትን ለመታደም በሄዱ ሰዎች ላይ መሆኑን ፓርቲው ጨምሮ ገልጿል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ጉዳዩ ባለመጣራቱ መረጃ መስጠት እንደማይቻል አስታውቋል።

የክልሉ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽሕፈት ቤት በበኩሉ በቤህነን አባላት ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት አስመልክቶ አቤቱታ እንዳልቀረበለት ገልጿል።