በሀገሪቱ ሰላም እንዲሰፍን ፀሎትና ምህላ ያስፈልጋል ተባለ

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነማትያስ በሀገሪቱ ሰላም እንዲሰፍን ፀሎትና ምህላ መደረግ አለበት ብለዋል። ፓትሪያሪኩ ይህንን ያሉት ሃይማኖታዊ የአክሱም ፅዮን በዓል ትናንት በከተማዋ በድምቀት በተከበረበት ግዜ ነው። የአክሱም ፅዮን በዓል የክርስትና እምነት ተከታዮች ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እና ከውጭ ሀገራት አማኞችና ጎብኚዎች በተገኙበት ተከብሯል።