አፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ ተፈጽመዋል ላላቸው ቀደምት በደሎች የካሳ ጥያቄ አነሳ

Your browser doesn’t support HTML5

ዛሬ በአዲስ አበባ በተጀመረው 38ኛው የመሪዎች ጉባኤ ላይ "የማካካሻ ፍትሕ" ጥያቄ ቀዳሚ አጀንዳ ሆኗል፡፡ በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ የማካካሻ ጥያቄው “የርዳታ ሳይኾን የፍትሕ ጥያቄ ነው” ብለዋል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ደግሞ “ለማካካሻ ፍትሕ ማዕቀፎች ጊዜው አሁን ነው” ሲሉ ጥያቄው መልስ እንዲያገኝ ጥሪ አቅርበዋል፡፡