ኢራን  ወደ እስራኤል ሚሳኤል ማስወንጨፏ ቀጣናውን ወደ ባሰ ትርምስ ይከተዋል - የዲፕሎማሲና አለም አቀፍ ግኑኝነት ተመራማሪ

Your browser doesn’t support HTML5

ኢራን ትናንት 180 ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል ካስወነጨፈች በኋላ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ተባብሶ ቀጥሏል።
በውጭ ጉዳይ የዲፕሎማሲ እና ዓለም አቀፍ ግኑኝነት ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ተመራማሪ ዶ/ር ዳር እስከዳር ታየ ኢራን በዋና አጋሯ ሂዝቦላ ላይ እስራኤል የወሰደችው ከባድ ወታደራዊ ርምጃ ሚሳኤል ለማስወንጨፏ ዋና ምክንያት ነው ይላሉ::

ይህ የቀጣናው ትርምስ ወደ ተባባሰ ሁኔታ ለመግባቱ መጀመርያ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው ያሉት ዶክተር ዳር እስከዳር እስራኤል ለጥቃቱ የምትሰጠው ምላሽም ቀጣይ ሁኔታውን የሚወስን ይሆናል ብለዋል::

አስማማው አየነው ነው ያነጋገራቸው፡፡