የኢትዮጵያ የሀገር ሽማግሌዎች መማክርት ጉባዔ

Your browser doesn’t support HTML5

በአማራና በትግራይ ክልሎች ፖለቲከኞች መካከል የሚታዩ አለግባባቶች ላይ የሚመክር የሽምግልና መድረክ ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በሽማግሎቹ ውይይት ላይ የተገኙት የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ፖለቲከኞችንም ሌሎችንም በመገሰፅ ጭምር ለሃገር ሰላምና ለመግባባት እንዲተጉ መልዕክት አስተላልፈዋል።