በአማራ ክልል ከሦስት ሚሊዮን በላይ ህጻናት የትምህርት ዕድል እንዳላገኙ ተገለፀ

Your browser doesn’t support HTML5

በአማራ ክልል በቅድመ አንደኛ ደረጃ እንዲሁም በአንደኛና መካከለኛ ደረጃ መማር ከሚገባቸው ህጻናት ውስጥ ከ3.2 ሚልዮን የሚልቁት ትምሕርት ቤት መገኘት እንዳልቻሉ የክልሉ ትምሕርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነት ጨምሮ፣ በተፈጥሮ አደጋ፣ በወረርሽኝና በቂ የትምህርት ተቋማት ባለመኖራቸው በርካታ ተማሪዎች በትምሕርት ዕድሜያቸው ማግኘት የሚገባቸውን ትምህርት እያገኙ አለመሆኑን ቢሮው ገልጿል፡፡

አሁን ያለው የጸጥታ ችግርና መፈናቀል ልጆቻችንን ወደ ትምህርት ቤት እንዳይልኩ እንቅፋት እንደፈጠረባቸው ለአሜሪካ ድምጽ አስተያየት የሰጡ ወላጆች ተናግረዋል፡፡

ትምህርት ቤት በመቆያቸው በመጠለያ ጣቢያ መኖራቸው እንደሚያሳዝናቸው የተናገሩም ህጻናት አሉ፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡