በሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ በድሌ ሮቃ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ገለጹ

Your browser doesn’t support HTML5

በሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ በድሌ ሮቃ መጠለያ ጣቢያ ተጠልለው የነበረው ተፈናቃዮች አጋጠመን ባሉት አሳሳቢ የምግብ እጥረትና ሰብአዊ ጉዳት ከመጠለያ ጣቢያው በመውጣት ወደ አጎራባች ከተሞች እየተሰደዱ መሆኑን ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየታቸውን የሰጡ ተፈናቃዮች ገለጹ፡፡

ተፈናቃዮቹ በሄዱባቸው ከተሞች በልመና ከመብላት እስከ በሸክም ሥራ ለመተዳደር መገደዳቸውን ጠቁመዋል፡፡

የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን በመጠለያ ጣቢያው የምግብ አቅርቦት እጥረት መኖሩን አረጋግጦ ችግሩ የተከሰተው ለጋሽ አካላት በገቡት ቃል መሰረት በወቅቱ እርዳታውን ማቅረብ ባለመቻላቸው ነው ብሏል፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ።