ለቀንዱ ስደተኞች ኹነኛ መፍትሔ እንዲፈለግ ተጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

በአፍሪካ ቀንድ እና በምሥራቅ አፍሪቃ ያሉት፣ ቁጥራቸው 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን የሚደርሱ ስደተኞች፣ የቀጣናውን ሀገራት ተፈናቃዮች ለማስተናገድ እና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት፣ ወደ ውስጣቸው ይመለከቱ ዘንድ ፍላጎታቸውን እየገለጡ ነው።

ሆኖም፣ በዩጋንዳዋ ዋና ከተማ ካምፓላ የተጀመረው እና ለአንድ ሳምንት የሚዘልቀው ጉባኤ ተሳታፊ ልዑካን፣ እንደ አለመቻቻል፣ አላዋቂነት እና የፖለቲካ ግጭት ያሉ ፈተናዎችን፣ በመንሥኤነት ይጠቅሳሉ።

ሃሊማ አቱማኒ ከካምፓላ ያጠናቀረችው ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።