በካሊፎርኒያ ተኩስ የከፈቱት ተጠርጣሪ ራሳቸውን ማጥፋታቸው ተገለፀ

Your browser doesn’t support HTML5

የጨረቃን ዑደት ተከትሎ በሚከበረው የቻይናውያን ሉናር አዲስ ዓመት ዋዜማ አንድ ታጣቂ በካሊፎርኒያ ግዛት ሞንቴሬይ ፓርክ ውስጥ በሚገኝ የዳንስ አዳራሽ ላይ በከፈቱት ተኩስ ወዲያውኑ 10 ሰው ሲሞት ሌሎች 10 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል። ጥቃቱን ፈጽመዋል ተብሎ የተጠረጠሩት የ72 ዓመት አዛውንት በማግስቱ ራሳቸው ላይ በተኮሱት ሽጉጥ ቆስለው መሞታቸውን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። የጥቃቱ ምክንያት እስካሁን በግልፅ አልታወቀም።

ለዝርዝሩ ዘገባውን የያዘውን ፋይል ይመልከቱ።