የሰላም ሥምምነቱ አተገባበር ሂደት ይበልጥ ግልፅ መሆን እንዲሆን ተጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

የሰላም ሥምምነቱ አተገባበር ሂደት ይበልጥ ግልጽ መሆን አለበት ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ዶ/ር ራሄል ባፌ ተናገሩ።

የሥምምነቱን የትግበራ ጅማሮ ያደነቁት ዶ/ር ራሄል ፤ “ነገር ግን ሰላሙ ዘላቂ እንዲሆን ትግበራው አካታች እና ግልጽ በሆነ መንገድ መካሄድ አለበት” ብለዋል፡፡

የመተማመን እጦት ለሰላም ሥምምነቱ ትግበራ እንቅፋት ሆኖ መቆየቱን የሁለቱም አካላት መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በትዊተራቸው ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጹሑፍ፣ ማንነቱን በግልጽ ባይጠቅሱም “ከመረብ ማዶ ያለው አመራር ልዩነት እንዲፈጠር የሚለምን ይመስላል” ብለዋል፡፡

የኤርትራ ኃይሎች ካለፈው ዓርብ ጀምሮ ከትግራይ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ለቀው እየወጡ መሆናቸውን ሮይተርስ መዘገቡ የሚታወስ ነው፡፡