የድምፅ መልዕክት ሰላምታን በመልዕክተኛ

Your browser doesn’t support HTML5

የስልክ እና የኢንተርኔት አገልግሎት በተቋረጠባት ትግራይ ክልል ለሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ሰላምታ ለማድረስ ድምፅ እየቀዱ እንደሚልኩ የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ይናገራሉ።

አዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ይህ ችግር እንዲቀረፍና ቤተሰቦቻቸውን እንዲያገኙ በክልሉ የተቋረጡት መሰረታዊ አገልግሎቶች ዳግም ሥራ እንዲጀምሩ ጠይቀዋል። ችግሩም ሰላማዊ መፍትሔ እንዲሰጠው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ከአንድ ዓመት በላይ ለሆነ ጊዜ በመለያየታቸውም የቤተሰቦቻቸው ሁኔታ እንደሚያሳስባቸው ገልፀዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።