ውድብ ናፅነት ትግራይ በመቐለ ውይይት እንዳያካሂድ መከልከሉን ገለፀ

Your browser doesn’t support HTML5

ውድብ ናፅነት ትግራይ ወይም "የትግራይ ነፃነት ፓርቲ" በመቐለ ከተማ ሊያካሂደው የነበረውን ሕዝባዊ ውይይት መከልከሉን ገለፀ፡፡ ፓርቲው ሕዝባዊ ውይይት ለማካሄድ ሲከለከል በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ሁለተኛው መሆኑን አስታውቋል፡፡ የመቐለ ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት በበኩሉ "ፓርቲው ያስፈቀደውም የሆነ የተከለከለ ስብሰባ የለም" በማለት ምላሽ ሰጥቷል፡፡