በቶሌው ጭፍጨፋ ላይ ሂዩማን ራይትስ ዋች ሪፖርት አወጣ

Your browser doesn’t support HTML5

ምዕራብ ኦሮምያ ውስጥ የሚንቀሳቀስ ታጣቂ ቡድን ባለፈው ሰኔ በመቶዎች የሚቆጠሩ አማርኛ ተናገሪ ሲቪሎችን መጨፍጨፉንና በወቅቱ የፀጥታ ኃይሎች እንዳልተከላከሉላቸው ዓለምአቀፉ የመብቶች ተሟጋች ቡድን ሂዩማን ራይትስ ዋች ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል።

ከጥቃቱ ለተረፉትም በቂ መጠለያ፣ ለጤናና ለደኅንነት ችግራቸውም መፍትኄ ሳይሰጥ ሦስት ወር ማለፉን ቡድኑ አክሎ አመልክቷል።

በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ ምርመራ እንደሚያስፈልግም ድርጅቱ ሂዩማን ራይትስ ዋች ጠቁሟል።