ደቡብ ክልል ለሁለት ተከፈለ

Your browser doesn’t support HTML5

ደቡብ ክልል የሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች በጋራ አንድ ክልል ለመመስረት ለኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ያቀረቡትን ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱ ደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች” የተሰኘ ክልል እንዲቋቋም ተወሰነ።

በሌላ በኩል ተቀራራቢ ዞኖች በአንድነት እንዲደራጁ መንግሥት ያቀረበውን ምክረ ሐሳብ ያልተቀበለው ጉራጌ ዞንን ጨምሮ በደቡብ ክልል ስር የሚገኙ ቀሪ አምስት ዞኖች እና አንድ ልዩ ወረዳ የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በሚል አንድ ክልል ሆነው እንዲቀጥሉ ተወሰነ።

የተለያዩ ገደቦች የተጣለበት ጉራጌ ዞን ከዛሬ ጀምሮ በኮማንድ ፖስት ሥር እንዲቆይ ተብሏል።