በኢትዮጵያ የጨቅላ ህጻናት ሞት

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ በቀን ከ324 በላይ ጨቅላ ህፃናት በሕክምና ሊቀረፉ በሚችሉ ችግሮች እንደሚሞቱ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ህፃናቱ የሚሞቱት ተገቢ የህክምና አግልግሎት ባለማግኘት፣ ኅብረተሰቡ ስለ ጨቅላ ህፃናት ባለው አመለካከት እና በእንክብካቤ ማነስ እንደሆነም አመልክቷል።

የጤና ሚኒስቴር የጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ እና ህፃናት ተገቢውን የህክምና አግልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል በሀገር አቀፍ ደረጃ በ80 ሆስፒታሎች ውስጥ ህክምናው እንዲሰጥ ማደረጉን የጤና ሚኒስቴር ደኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ገልጸዋል።