ባሕር ዳር የታሰረው የቀድሞ አል - ዐይን ዘጋቢ ወደ ዐዲስ አበባ ተዛወረ

Your browser doesn’t support HTML5

በልዩ ልዩ የአገር ውስጥ እና የዓለም አቀፍ ብዙኃን መገናኛዎች ላይ በዘጋቢነት የሠራውና፣ በአኹኑ ወቅት “አራት ኪሎ ሚዲያ” የተሰኘ ዩቲዩብ አዘጋጅ የኾነው ዳዊት በጋሻው፣ ትላንት፣ በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር ከዋለበት ባሕር ዳር ወደ ዐዲስ አበባ ተመልሶ በእስር ላይ እንደሚገኝ፣ ባልደረባው አልዓዛር ተረፈ ተናግሯል፡፡

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ማኅበር፣ ዳዊት በጋሻው ከእስር እንዲለቀቅ ጠይቋል፡፡ ዳዊት በጋሻውን ጨምሮ ፣ የዩቲዩብ ብዙኃን መገናኛ ባለሞያዎች ሰሞኑን በጸጥታ ኃይሎች በተከታታይ እየታሰሩ መኾኑ ታውቋል።

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።