ፊሊፖ ግራንዲ ዳባት ላይ ከስደተኞች ጋር ተወያዩ

Your browser doesn’t support HTML5

በሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ የሚገኘውን "አለም ዋጭ” የኤርትራ ስደተኞች ጣቢያ የጎበኙት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ ከስደተኞቹ ተወካዮች ጋር ውይይት አካሂደዋል።

በውይይቱ ስደተኞቹ የተጓደሉ መሰረተ ልማቶች እንዲሟሉላቸው ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ቃል አቀባይ በአካል ንጉሴ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት የለጋሾች ድጋፍ እንደሚያስፈል ተናግረዋል።

ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።