የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን አባላት ወደ ትግራይ ሊላኩ ታቅዷል

Your browser doesn’t support HTML5

ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሁሉንም አካባቢዎችና የኅብረተሰብ ክፍሎች ለማካተት በሚያደርገው ጥረት ግጭት ያለባቸውን አካባቢዎችም ለመድረስ እየሠራ እንደሚገኝ የኮሚሽኑ አባል ዶ/ር ዮናስ አዳዬ ለቪኦኤ ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራትና የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ላይ በሚኖራቸው ሚና ላይ ዛሬ፤ ማክሰኞ ተወያይተዋል።

የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የኮሚሽኑን ዓላማ ከግብ ለማድረስ በትብብር እንደሚሠሩ ገልፀዋል።

/ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/