በአምቦ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ጉዳት ደረሰ

Your browser doesn’t support HTML5

በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የአንድ ተማሪ ህይወት ማለፉን ተከትሎ በአምቦ ዩኒቨርሲቲም በተማሪዎችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት አሥር ተማሪዎችና ሦስት የፀጥታ አካላት መቁሰላቸውን የዩኒቨርሲቲው ሪፈራል ሆስፒታል ገለፀ። የሣይንስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር "አለመረጋጋት ተፈጥሮባቸው ከነበሩ 22 ዩኒቨርስቲዎች ከ7 ውጭ ሌሎቹ ተረጋግተዋል" ብሏል። የቀሩትም ተረጋግተው ወደ ቀድሞ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲመለሱየኅብረተሰቡን ትብብር ጠይቋል።