የአል-ሻባብ መሪ አብዲ ጎዳኔ ተገድሏል

  • ቪኦኤ ዜና
የአል-ሻባብ መሪ አህመድ አብዲ ጎዳኔ መገደሉን የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት አረጋገጠ።

አህመድ አብዲ ጎዳኔ /ፎቶ ከኢንተርኔት የተገኘ/

Your browser doesn’t support HTML5

የአል-ሻባብ መሪ አብዲ ጎዳኔ ተገድሏል

የአል-ሻባብ መሪ አህመድ አብዲ ጎዳኔ መገደሉን የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት አረጋገጠ።

አህመድ አብዲ ጎዳኔ ባለፈው ሰኞ፤ ነኀሴ 26/2006 ዓ.ም ደቡብ ሶማልያ ውስጥ በተካሄደው የዩናይትድ ስቴትስ የአይሮፕላን ጥቃት መገደል አለመገደሉን ሲያጣሩ ሰንብተዋል፡፡

ዛሬ ዐርብ፤ ነኀሴ 30/2006 ዓ.ም ማምሻው ላይ ከዋይት ኀውስ ይፋ በሆነው ዜና መሠረት ጎዳኔ በአየር ድብደባው መገደሉን የዩናይትድ ስቴትስ መከላከያ ሚኒስቴር አረጋግጧል፡፡

አህመድ አብዲ ጎዳኔ /ፎቶ ከኢንተርኔት የተገኘ/

የዐይን ምስክሮችም የዩናይትድ ስቴትስ ድሮን ደቡብ ሶማልያ ውስጥ በሚገኙ የአል-ሻባብ መሪዎች ላይ የሚሳይል ጥቃት ማካሄዱን ተናግረዋል።

ጎዳኔ፣ አል-ሻባብን እአአ ከ2008 ዓም አንስቶ ይመራ የነበረ ሲሆን ዩናይትድ ስቴትስም እጁን ይዞ ለፍርድ ላቀረበ ወይም የሚገኝበትን ለጠቆመ የሰባት ሚልየን ዶላር ወሮታ ለመክፈል ቃል ገብታ ነበር።

«የጎዳኔ መገደል በሽብርተኛነት ላይ የተገኘ ከፍተኛ ድል ነው» ያለው ዋይት ኀውስ «አፍሪቃ ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ የአል-ቃዒዳ ተለጣፊ አማፂያን ደግሞ ትልቅ ኪሣራ ነው» ብሏል።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ከሥር ያሉትን ማገናኛዎች እየተጫኑ ይከተሉ፡፡

http://www.whitehouse.gov/the-press-office/2014/09/05/statement-press-secretary-death-ahmed-godane

http://www.defense.gov/news/newsarticle.aspx?id=123096

http://www.rewardsforjustice.net/english/most-wanted/all-regions.html

http://www.rewardsforjustice.net/english/ahmed_aw_mohamed.html

https://twitter.com/TheVillaSomalia/status/507947220847443968