የዓድዋ ድል በዋሽንግተን ዲሲ በልዩ ዝግጅት ተከበረ

Your browser doesn’t support HTML5

በዋሺንግተን ዲሲ እና አካባቢው የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ የዓድዋ ድል በዓልን 127ኛ ዓመት፣ ትላንት ምሽት በተከናወነ ልዩ ዝግጅት አክብረዋል።

በዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ በነበረው የበዓሉ አከባበር ዝግጅት፣ ታሪካዊው ድል ያለው ፋይዳ ተዘክሯል፤ ልዩ ልዩ ኪነ ጥበባዊ መሰናዶዎችም ቀርበዋል።