አዴፓ የብልፅግና አካል ለመሆን ወሰነ
Your browser doesn’t support HTML5
የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /አዴፓ/ ወደ ብልፅና ፓርቲ የሚያደርገውን የኢሕአዴግ ውኅደት በሙሉ ድምፅ አፀደቀ። ፓርቲው ውኅደቱን ያፀደቀው ቀደም ሲል በኢሕአዴግ ሥራ አስፈፃሚ እና በምክር ቤቱ የተላለፈውን ውሣኔ ተከትሎ ነው የኢሕአዴግ ሊቀ መንበርና የሃገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባሠፈሩት የፌስቡክ መልዕክት አዴፓ እና ኦዴፓ የብልፅግና ፓርቲን ለመቀላቀል መወሰናቸውን ይፋ አድርገዋል።